Sunday, November 3, 2013
በኢትዮጵያ ውስጥ መቸቻልና እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ እርቅና የሽግግር መንግስት ማቋቋም ቅድሚያ ሰጥተን ልንተገብረው የሚገባ ብቸኛው የቤት ስራቾን ነው።በማን አለብኝና በእብሪት የተሞላ የጠመንጃ አምልኮ ለአንዴና ለመጨረሻ ከታሪካቸችን መፋቅ አለበት። ኢትዮጵያ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩል የምታስተናግድ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ አገር ትሆን ዘንድ ከጥላቻና ከመጠላለፍ የዘር በሽታ ተላቀን ያለፈውን የታሪክ ምዕራፍ ፍፁም በሆነ ይቅርታና ፍቅር መዝጋት አለብን። የዛሬው የትናንቱን ሲኮንን፣ የነገው ደግሞ የዛሬውን እየኮነነ በድግግሞሽ የታሪክ ሽክርክሪት ውስጥ ከመኖር ወጥተን እውነተኛ ወንድማማችነት የሰፈነበት የፍቅርና የመቻቻል የፖለቲካ ባህል መገንባት ከቻልን አሁን የምናያት ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከአደጉት አገሮች ተርታ በአኃዝ ሳይሆን በተግባር የምትሰለፍበት ቀን እሩቅ አይሆንም። ስለዚህ ጥላቻን፣ መነናቅን፣ ዘረኝነትን፣ ጠባብነትን፣ አስወግደን እንደ አንድ ህዝብ በጋራ ተሰልፈን ድህነትን ከአገራችን ለማጥፋት መረባረብ ይኖርብናል። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment