Saturday, November 2, 2013

የኢትዮጵያ ህዝብ ለመለስ ፋውንዴሽን ጆሮዉንም እዩንም አንደነፈገ ታወቀ

የህወሀት መስራችና የረጂም ግዜ መሪ የነበረዉ ዘረኛዉ መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት በተለየ በስምንት ወሩ ባለፈዉ መጋቢት መጨረሻ ላይ ይፋ ሆኖ የተመሰረተዉ የመለስ ፋውንዴሽን ከህዝብ ያገኛል ተብሎ የተገመተዉን የገንዘብ መዋጮ የሩቡን ግማሽም አለማግኘቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በሰልክ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገለጹ፡፡ በመለስ ፋውንዴሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 781/2005 መንግስታዊ ተቋም ሆኖ የተመሰረተው ይህው ፋውንዴሽን ቤተመጻህፍትና ሙዚየም ለማቋቋም በማሰብ ሕዝቡ ገንዘብ እንዲያዋጣ በየቀኑ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ቅስቀሳ ከተጀመረ ከአምስት ወራት በላይ ቢቆጠርም እየተዋጣ ያለው ገንዘብ እጅግ አነስተኛ መሆኑ ታውቋል፡፡
ህዝብ በያለበት ለመለስ ፋዉንዴሺን የገንዘብ መዋጮ ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነዉ ፋውንዴሽኑን በበላይነት የምትመራዉና የሙስናዋ እመቤት በመባል የምታወቀዉ አዜብ መስፍንና ሟቹ ባለቤቷ ከህዘብ ዘርፈዉ በውጪ አገር ባንኮች ከፍተኛ ገንዘብ ማከማቸታቸዉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንና በውጪ አገር የሚገኙ የኢትዮጽያ መገናኛ ብዙኋን በተደጋጋሚ በመዘገባቸዉ እንደሆን ብዙዎች በመናገር ላይ ናቸዉ። ከዚህ በተጨማሪ አብዛኛው የመንግስት ሰራተኛና የግሉ ዘርፍ ለህዳሴዉ ግድብ ገንዘብ እያዋጡ መሆናቸዉና ህዝቡ መለስ ዜናዊን ለመሰለ ሃያ አንድ አመት ሙሉ ለረገጠዉ ጨቋኝና ከፋፋይ ሰዉ የገንዘብ መዋጮ ማድረግ ባለመፈለጉ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። የአዲሰ አበባ ምንጫችን ጨምሮም እንደገለጸዉ መዋጮው በውዴታ በባንክ ገቢ የሚደረግና ለጋሹ ስሙን ከማስመዝገብ በላይ መስጠትና አለመስጠቱ የማይታወቅ በመሆኑ ከፍተኛ የግንባሩ ካድሬዎችና ራሳቸውን የኢህአዴግ ደጋፊ ባለሃብቶች ነን የሚሉት ሳይቀሩ ለመዋጮው እጃቸውን አለመዘርጋታቸው መረጃው ያሳያል።

በባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ ነው
ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ካለፉት 4 ቀናት ጀምሮ በከተማዋ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ እንደሆነ የዘጋብያችን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ዛሬ በከተማዋ መውጫና መግቢያ በሮች ላይ ሰዎች ከመኪናዎች እና ባጃጆች ላይ እንዲወርዱ እየተደረገ በጥብቅ ተፈትሸዋል።
አንዳንድ ወገኖች መንግስት ጸረ ሰላም እና አሸባሪዎች በከተማዋ ገብተዋል የሚል ወሬ እንደሚያስወራ ሲገልጹ፣ ሌሎች ነዋሪዎች ደግሞ የከተማውን ህዝብ ለማስበረገግ ሆን ብሎ መንግስት የሚያደርገው ነው ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ በቅርቡ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ እንደደረሰው አይነት የተቀነባበረ ፍንዳታ ሊከሰት ይችላል የሚል አስተያየቶች ይቀርባሉ።
የፌደራል ፖሊሶች በሚያካሂዱት ፍተሻ ህዝቡን እያንገላቱ መሆኑንም ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በጉዳዩ ላይ የከተማውን የፖሊስ አዛዦች ለማነጋገር ብንሞክርም አልተሳካልንም።
በአዲስ አበባ በቅርቡ የከሸፈውን ፍንዳታ በተመለከተ የመስተዳድሩ ፖሊስ ኮሚሽነር ይኸደጎ ስዩም ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በህዝቦቹ ላይ ድራማ የሚሰራበትና የሚቀልድበት ምንም ምክንያት የለውም በማለት መናገራቸው ይታወቃል።
ኮሚሽነሩ ፍንዳታው ቅንብር ነው በማለት የሚናገሩትን ፖለቲከኞችንም ወቅሰዋል።
ዊኪሊክስ ይፋ ባደረገው መረጃ የአሜሪካ ኢምባሲ የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ የሽብር አደጋ አለ ለማስባል ፣ ሆን ብሎ ፍንዳታዎችን ያቀናብራል ብሎ እንደሚያምን መግለጹ ይታወሳል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህርዳር አንድ የባጃጅ ሹፌር በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ ተገኝቷል። የቀበሌ 7 ነዋሪ የሆነው ወጣት አይኖቹ ወጥተውና በከፍተኛ ሁኔታ ተደብድቦ ከቀናት በሁዋላ ነው ሞቶ የተገኘው። የከተማው ፖሊስ ኮሚሽን በግድያው ዙሪያ እስካሁን የሰጠው አስተያየት የለም።
Like · 
በባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ ነው
ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ካለፉት 4 ቀናት ጀምሮ በከተማዋ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ እንደሆነ የዘጋብያችን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ዛሬ በከተማዋ መውጫና መግቢያ በሮች ላይ ሰዎች ከመኪናዎች እና ባጃጆች ላይ እንዲወርዱ እየተደረገ በጥብቅ ተፈትሸዋል።
አንዳንድ ወገኖች መንግስት ጸረ ሰላም እና አሸባሪዎች በከተማዋ ገብተዋል የሚል ወሬ እንደሚያስወራ ሲገልጹ፣ ሌሎች ነዋሪዎች ደግሞ የከተማውን ህዝብ ለማስበረገግ ሆን ብሎ መንግስት የሚያደርገው ነው ይላሉ። በሌላ በኩል ደግሞ በቅርቡ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ እንደደረሰው አይነት የተቀነባበረ ፍንዳታ ሊከሰት ይችላል የሚል አስተያየቶች ይቀርባሉ።
የፌደራል ፖሊሶች በሚያካሂዱት ፍተሻ ህዝቡን እያንገላቱ መሆኑንም ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በጉዳዩ ላይ የከተማውን የፖሊስ አዛዦች ለማነጋገር ብንሞክርም አልተሳካልንም።
በአዲስ አበባ በቅርቡ የከሸፈውን ፍንዳታ በተመለከተ የመስተዳድሩ ፖሊስ ኮሚሽነር ይኸደጎ ስዩም ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በህዝቦቹ ላይ ድራማ የሚሰራበትና የሚቀልድበት ምንም ምክንያት የለውም በማለት መናገራቸው ይታወቃል።
ኮሚሽነሩ ፍንዳታው ቅንብር ነው በማለት የሚናገሩትን ፖለቲከኞችንም ወቅሰዋል።
ዊኪሊክስ ይፋ ባደረገው መረጃ የአሜሪካ ኢምባሲ የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ የሽብር አደጋ አለ ለማስባል ፣ ሆን ብሎ ፍንዳታዎችን ያቀናብራል ብሎ እንደሚያምን መግለጹ ይታወሳል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህርዳር አንድ የባጃጅ ሹፌር በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ ተገኝቷል። የቀበሌ 7 ነዋሪ የሆነው ወጣት አይኖቹ ወጥተውና በከፍተኛ ሁኔታ ተደብድቦ ከቀናት በሁዋላ ነው ሞቶ የተገኘው። የከተማው ፖሊስ ኮሚሽን በግድያው ዙሪያ እስካሁን የሰጠው አስተያየት የለም።
Like · 

I miss being a little kid


I miss being a little kid with no stress worries, 
or care in the world.
- See more at: http://www.awesomequotes4u.com/2013_10_01_archive.html#sthash.XHm8NPpK.dpuf

በወያኔ ሎሌነት ከመማቀቅ አንድ ቀን ነፃ ሆኖ መኖር ይሻላል

በወያኔ ግፈኛ ስርአት መከራቸውን ከሚያዩ ዜጎች ውስጥ ራሱ ሥርአቱ ለራሱ መገልገያ የሰበሰባቸውና ያሰማራቸው ዜጎች ይገኙበታል። ከእጅ ወደ አፍ እንኳን ለማትሆን ደመዎዝ በሰራዊቱ ውስጥ በተራ ወታደርነትና በበታች ሹማምንት የሲኦልና የጉስቅልና ኖሮ እንደሚኖሩ እናውቃለን።
በየዞኑና በየወረዳው በካድሬነት ወያኔ ለገላጋይነት ያሰማራቸው ሰራተኞችና የድርጅቱ አባሎች ከህዝቡ የጥላቻ ሰለባነት ባልተናነሰ በኑሮአቸው ለራሳቸውም ለቤተሰቦቻቸውም ሳያልፍላቸው እንደሚኖሩ እናውቃለን።
ይልቁንስ የወያኔው የአመራር ጉጅሌ ነገ የት እንደሚያደርሳቸው በማያውቁት ጨለማ ውስጥ ነው የሚዳክሩት ሚስጥርና የዳጎሰ ጥቅም ከነሱ ዘንድ አይደርስም። በቀድሞ ጊዜ የነበሩት የባላባት ሎሌዎች እንኳን ክብር አላቸው።
በዚህ ላይ ሁሉም አስተማማኝ ሎሌ መሆኑን ወያኔ ለማረጋገጫ የሚጠቀምበት ግምገማ አለ። የወያኔ ግምገማ የበታች አባላትና ደጋፊዎቹን በማስፈራራት ያላቋረጠ ድጋፍ እንዲሰጡት የሚያደርግበት በመሰረቱ ከውሻ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የማይለይ ተቋም ነው። የትምህርት እድል የስራ እድገትና የደመወዝ ጭማሪ የወያኔው ጉጅሌ የባርነት መደለያዎች ናቸው።
ግንቦት 7 ከጥቂት ከመንገዳቸው እያወጡ ህዝብ ከሚያሰቃዩት የወያኔ ታዛዥ ሎሌዎች በቀር የሀገርና የወገን ጠላት ናቸው ብሎ አያምንም። ትግላችን ለነሱም ነጻነት ነው። እነዚህ ወገኖቻችን ባገኙት አጋጣሚና እድል ሁሉ ትግሉን ያግዛሉ ብሎም ያምናል። የሚያግዙም አሉ። እርግጥ ነው ባሽከርነት ኑሮ የተንገፈገፉ የሰራዊቱ አባላትና ለህሊናቸው ክብር ያላቸው በርካታ የስርአቱ አገልጋዮች ትግላችንን እየተቀላቀሉ ነው።
ግንቦት 7 ንቅናቄ ዛሬም እንደሁሌው ለነዚህ ወገኖች ኑ ተቀላቀሉን የሚል ጥሪውን ያቀርባል። ሁላችንም ከነክብራችን ሆነን ሰዎችን ሳይሆን ውዲቱን ሀገራችንና ህዝባችንን በፈቃደኝነት በነጻነት የምናገለግልበት ጊዜ እየቀረበ ነው፡፡
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!


የስሚንቶ ፋብሪካዎች የገበያ ችግር እንዳጋጠማቸው ተዘገበ

ጥቅምት (ሃያ)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :- ሪፖርተር ዛሬ ባወጣው ዘገባ በአገሪቱ የሚገኙ ሶስቱ ታላላቅ ስሚንቶ ፋብሪካዎች በአመት 12 ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ የማምረት አቅም ቢኖራቸውም በገበያ ውስጥ የሚገኘው ስሚንቶ ድምር ከ5 ሚሊዮን አይበልጥም።
አብዛኛውን ስሚንቶ የሚገዛው መንግስት ሲሆን፣ የግሉ ዘርፍ ድርሻ ቀዝቃዛ መሆኑ ተዘግቧል።
የሼክ ሙሀመድ አላሙዲን ንብረት የሆነው ደርባን ኩባንያ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ በኩንታል 209 ብር እየሸጠ፣ ለደንበኞቹ ቤታቸው ድረስ እያደረሰ ነው። ሙገር ስሚንቶም በተመሳሳይ ለልዩ ደንበኞቹ ምርቶቹን ቤታቸው ድረስ እያደረሰ ነው።
ለሪፖርተር አስተያየታቸውን የገለጹ ባለሙያዎች ” ብዙም ግልጽ ባልሆነ ምክንያት የሲሚንቶ ገበያ እየተቀዛቀዘ መጥቷል፡፡ በዚህም ምክንያት በ2006 ዓ.ም 21 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን፣ በ2007 ዓ.ም. 27 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ አገሪቱ እንደምትፈልግ ከአራት ዓመት በፊት የወጣው ጥናት ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡
‹‹ለሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ ከፍተኛ የካፒታል ኢንቨስትመንት ፈሷል፤›› ሲሉ አስተያየታቸውን የሚሰጡት ባለሙያዎች፣ ጉዳዩን መንግሥት ከሥሩ ሊያጤነው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በዚህ ሁሉ መሀል መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ 70 በመቶ የሚሆነውን ምርቱን ለአባይ ግድብ እና ለግልገል ጊቤ 3 የሀይል ማመንጫ ግድቦች በማቅረብ ላይ ነው። መሰቦ ሲሚንቶ በምን መስፈረት ለአባይ ግድብ ግንባታ አቅራቢ ሆኖ እንደተመረጠ አልታወቀም። ሙገር ስሚንቶ የመንግስት  ወይም የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ንብረት ሆኖ ሳለ፣ እንዲሁም ለአባይ ግድብ ማሰሪያ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ  በውድም በግድም ገንዘብ እንዲያዋጣ እየተደረገ ፣ ለድርጅቱ ስሚንቶ የሚያቀርበው ሙገር መሆን ሲገባው የህዝባዊ ወያን ሀርነት ትግራይ ኩባንያ የሆነው መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ እንዲሆን መደረጉ ” የኢትዮጵያ ህዝብ ያዋጣል፣ ገቢው ወደ ህወሀት ኪስ ይገባል” ሲል አስተያየቱን የተጠየቀው የኢሳት የአዲስ አበባ ዘጋቢ ገልጿል።
ህዝቡ ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ገንዘብ እንዲያዋጣ ቢገደድም፣ ገንዘቡ በተዘዋዋሪ መንገድ ወደ ህወሀት ካዝና ነው የሚገባው የሚለው ዘጋቢያችን፣ መስፍን ኢንጂነሪንግና የወ/ሮ አዜብ መስፍን የእህት ልጅ ንብረት የሆነው ወርኪድ የተለያዩ የግንባታ እቃዎችንና የብረታ ብረት ውጤቶችን በማቅረብ ከግድቡ ከፍተኛ ገቢ እያገኙ ነው ብሎአል።
ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን ለአባይ ግድብ ለማዋጣት 500 ሚሊዮን ብር  ቃል ቢገቡም በተለያዩ ሰበቦች እስካሁን አጠናቀው አልከፈሉም።  ዘጋቢያችን  ምናልባትም ኩባንያቸው ደርባን ለግድቡ ስሚንቶ እንዳያቀርብ በመከልከሉ ተበሳጭተው ሊሆን ይችላል ብሎአል።

ሕዝባዊ እምቢተኝነት በውጭ አገር፤ እንዴት?

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሁለገብ ትግል ወያኔ ማስወገድ ይገባል ብሎ የሚያምና ለዚህም የሚታገል ድርጅት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል ሰላማዊም ሰላማዊ ያልሆኑም የትግል ስልቶችን መጠቀም ማለት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም የሚደረጉ ትግሎች ማለት ነው።
ከዚህ አንፃር በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሚና ምን ሊሆን ይገባል?
በግንቦት 7 እምነት በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በድጋፍ ሰጭነት ሳይወሰኑ የትግሉ ቀጥተኛ ተሳታፊዎች መሆን ይኖርባቸዋል። በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በወያኔ ጥቅሞችና ተቋማት ላይ በማመጽ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አርዓያ መሆን ይኖርባቸዋል።
በዚህ ረገድ የተጀመሩ አበረታች ጥረቶች አሉ፤ ለምሳሌ:
  1. ወያኔ ሙስሊሞችን ከክርስቲያኖች ለማጣላት ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን “እንቢ አንጣላልህም” ያሉት መሆኑ የሚያኮራ ነው። ወያኔ ከጠበቀው በተቃራኒ የሁለቱም ሃይማኖቶች መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ ሲመክሩ መታየቱ ተስፋ ሰጪ ጅማሮ ነው። አብሮነታችንን ማጎልበትና ይህንን በአደባባይ፣ በአዳራሾች፣ በቴሌቪዥን መስኮቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳየት እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው። ውጭ የተጀመረው አገር ቤት መዳረሱ የማይቀር ነው። ይህ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርብናል።
  2. ወያኔ በአባይ ግድብ ስም በውጭ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በርከት ያለ ገንዘብ እንደሚያገኝ ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያን “ከአባይ በፊት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይገደብ” “ከአባይ በፊት ሙስና ይገደብ” እያሉ ወዋጮዎቹን እንቢ ብለዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን የታየው ጽናት በጣም አበረታች ነው። የወያኔ ሹማምንት በአባይ ጉዳይ እንኳንስ ገንዘብ ስብሰባም ሊሰበሰቡ አልቻሉም። ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
  3. ኢትዮጵያዊያን በስፖርትና በኪነጥበባት መስኮች የሚያደርጓቸው መሰባሰቦች ለትግሉ ትልቅ እገዛ ይሰጣሉ። የኢትዮጵያ ስፓርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ (ESFNA) ከወያኔና ከወያኔ ሸሪክ ቱጃር ጋር ያደረገው ትንንቅ የሚያኮራ ነው። በርካታ ኢትዮጵያዊያን አገር፣ ነፃነት፣ ክብር ይበልጥብኛል ብለው የቀረቡላቸውን አጓጊ ማባበያዎችን “እንቢ” ብለዋል። ይህ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
  4. ባለፈው ዓመት ጋዜጠኛ አበበ ገላው በመለስ ዜናዊ ላይ፤ ዘንድሮ ደግሞ ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድና አቶ መስፍን የዘረኛው ወያኔ ግንባር ቀደም አስተባባሪ በሆነው ስብሀት ነጋ ላይ ያሰሙት ተቃውሞ በጣም የሚደገፍና በውጭ አገራት የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ባህል ሊሆን ይገባዋል።
  5. በስዊድን የሚገኙ የሕግ ባለሙያዎች የጀመሩት እና በኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ተሳትፎ እየተካሄደ ያለው የወያኔ ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ የማቅረብ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።
እነዚህ መልካም ሥራዎች ምሳሌቶች ሲሆኑ በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ በላይ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። አንዳንዱን ለአብነት ያህል ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል።
  1. በአገራችን ውስጥ መሠረታዊ የሆነ ለውጥ እንዲመጣ ከፈለግን ወያኔን ማስደንገጥ፣ ማሸበር፣ ካስፈለገም ማስወገድ የሚችል የአመጽ ኃይል መኖሩ ወሳኝ ነው። እንዲህ ዓይነት የወገን ኃይል ከጀርባው መኖሩ ሲሰማው ነው ሕዝብ ለእንቢተኝነት የሚነሳሳው። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ኃይል ቢቻል መቀላቀል፤ ካልተቻለም በአባላት ምልመላ፣ በፋይናንስ፣ በሎጂስቲክስና ዲፕሎማሲ መደገፍ ይጠበቅባቸዋል። ይህ ከሁሉ የላቀ የእምቢተኝነት መገለጫ ነው።
  2. ትግሉ እየመረረ መሆኑ በመረዳት በርቀት ሆነን ከመብሰክሰክ በትግል ላይ ያሉትን ድርጅቶች መቀላቀል ሌላው አሁኑኑ ልናደርገው የሚገባ ነገር ነው። ድርጅቶች “አይረቡም” ብለን ስላጣጣልናቸው አይጠናከሩም። ድርጅቶችን ማጠናከርና ማዘመን ያለብን እኛው ነው። መሪዎችን ማውጣት ያለብን እኛው ነው። እስካሁን ድርጅቶችን ያልተቀላቀልን ካለን መቀላቀልና ትግሉን ማጧጧፍ ይኖርብናል።
  3. በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ወያኔን “እንቢ” እንበል። “እንቢ” የማለትን አጋጣሚ ማሳለፍ የለብን። “እንቢ” ማለት የምንችልባቸው አጋጣሚዎች ብዙዎች ናቸው። ለምሳሌ: -
ሀ) ወያኔ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታን አዲስ የገንዘብ ማለቢያ ለማድረግ አቅዶ ተነስቷል። ወደ ሚሊዮን የሚጠጉ ቤቶችን በ2 ዓመት ጨርሼ አስረክባለሁ በሚል ማባበያ በውጭ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ለመሰብሰብ ዝግጅቱን አጠናቋል። ይኸንን ነገር አጠንክረን “እንቢ” ማለት ይኖርብናል። “ለኛ ቤት ከመሰጠቱ በፊት፤ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን መወደቂያ ያግኙ” ማለት ካልቻልን በራሳችን ማፈር አለብን። የአውሮፓና የአሜሪካ መንግሥታትን አምባገነኖችን በገንዘብ አትደግፉ እያልን እኛ ራሳችን ወያኔን በገንዘብ የምንደግፈው ከሆነማ ከነሱ ብሰን መገኘታችንን እንወቀው።
ለ) ወያኔ በስደተኛ ስም በመካከላችን የሰገሰጋቸውን ካድሬዎችን የማጋለጥ ዘመቻ ማፋፋም አለብን። የወያኔ ደጋፊዎችን በኤርትራ ስደተኞች ስም እንደሚገቡ መረጃዎች አሉ። በደል ደርሶብናል ብለው መንግሥታትን አሳምነው የመኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ አጠቃን ካሉት አገዛዝ ጋር የሚሠሩ መሆናቸው የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን አጠናቅረን ለየሀገሩ መንግሥታ ማቅረብ እንደ አቢይ ሥራ መያዝ ይኖርብናል።
ሐ) የወያኔ ባለሥልጣናት የሚገዟቸውን ቤቶች፤ የሚያስተዷድሯቸውን ቢዝነሶች እያደንን ማጋለጥ ይኖርብናል።
መ) የወያኔዎች ሹማምንት በአሜሪካና አውሮፓ በነፃነት ሊዘዋወሩ አይገባም። በሄዱት ሁሉ ተቃውሞና ውርደት ሊከተላቸው ይገባል።
ሠ) የወያኔ ቢዝነሶች ላይ ማዕቀብ ማድረግን (ቦይ ኮት) መልመድ አለብን። ጥረቶቻችንን በፈጠራ ከደገፍን ወደ አገር ቤት የምንልከው ገንዘብ የወያኔ የውጭ ምንዛሬ ረሀብ ማስታገሻ የማይሆንበት መንገድ መሻት አለብን።
ረ) ለወያኔ ባለሥልጣኖች ዲግሪ የሚያድሉ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማዋረድ መጀመር አለብን። ስምንተኛ ክፍል እንኳን በወጉ ላልጨረሱ ሰዎች የማስትሬት ዲግሪ እንደሰጡ ማሳወቅ የኛ ኃላፊነት መሆን አለበት።
በግንቦት 7 እምነት ትግሉ በሁሉም ሥፍራ ነው። ኢትዮጵያዊያን በያለሉበት ቦታ በተደራጀና በተቀናጀ መልክ ወያኔን ፊት ለፊት ከተጋፈጥን የድላችን ቀን እናቀርባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!



    Educated Ethiopians are joining armed movements (Andargachew Tsige)

    http://www.youtube.com/v/C3wmeYHMc6g?version=3&autohide=1&autohide=1&feature=share&showinfo=1&autoplay=1&attribution_tag=Y434PH65YrfzCpCt6aANOw